የሰው ሀብት ልማት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ተግባርና ሃላፊነት
- በሚቀርብ የቅጥር ጥያቄ መሰረት መመሪያን መሰረት አድርጎ የሰራተኛ ቅጥር ይፈጽማል
- የሰራተኛ ቅጥር የክልሉ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እና የፕሮግራሞች የሰው ሀይል አሰተዳደር መመሪያ አሰራር በሚያዝዘው መሰረት ብቻ እንዲፈጸም ክትል ያደርጋል
- የሰራተኞችን ጥያቄ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እና የፕሮግራሞች የሰው ሀይል መመሪያ በሚያዝዘው መሰረት በጽሁፍ ወቅታዊ ምላሽ ይሰጣል፤
- የሰራተኛውን የአቅም ግንባታ እና ስልጠና ያቅዳል ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን አፈጻጸሙን ይከታተላል የተሟላ መረጃ ይይዛል፤
- ልዩ ልዩ የመደብ፣ የትምህርት ዝግጅትና ጥቅማጥቅም ጥያቄዎችን በማሰባሰብና በመሰነድ ቢሮው ምላሽ እዲሰጥ ያደርጋል፤
- በመደብ፣ በደረጃ ዕድገት እንዲሁም ጥቅማጥቅምና ሌሎች የሚነሡ የሠራተኛ ጥያቄዎች በየደረጃው ለሲቪል ሠርቪስ ተቋማት ቀርቦ መታየትና ችግሮች ካልተፈቱ ተዋረዱን ጠብቆ ውሳኔ እየተሰጣቸው መምጣት ይኖርበታል፤
- አጠቃላይ የሰው ሃይል መመሪያን መሰረት አድርጎ ይሰራል፤
- ለቢሮው ተጠሪ ለሆኑ ተቋማት ድጋፍና ክትትል ያደርጋል፤
2. የመንግስት_ተቋማት_የለውጥ_አመራር፣አደረጃጀትና_አሰራርን_ለመሻሻል_የወጣውን_መመሪያ_ቁጥር_50_2014.pdf
3. የመንግስት_ሰራተኞች_የስራ_አፈፃፀም_ለመመዘን_የወጣ_መመሪያ_ቁጥር_49_2014_ዓም_rotated.pdf