የዕቅድ፣ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ተግባርና ሃላፊነት

  • የተቋሙን የረዥምና የአጭር ጊዜ ዕቅድ ከሚመለከተው ጋር በመሆን ያዘጋጃል፣ ያስገመግማል፤
  • የተቋሙን የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያዘጋጃል፣ ያስገመግማል፣ ለሚመለከተው አካል ያስተላልፋል፤
  • የበጀት ምደባ፣ ግምገማና አፈጻጸም ይከታተላል፤
  • የበጀት ዝውውርን መመሪያን መሠረት አድርጎ ያዘጋጃል፣ እንዲጸድቅም ክትትል ያደርጋል፤
  • አጠቃላይ የፊዚካልና የፋይናንሻል አፈጻጸምን ከቢሮው ዕቅድ ጋር አያይዞ ክትትል ያደርጋል፣ ይገመግማል፣ ሪፖርት በመዘጋጀት ለሚመለከተው አካል ያቀርባል፤
  • የመስኖ ልማት መረጃና ኢንፎርሜሽን ሥርዓትን ይዘረጋል፣ ያደራጃል፣ መረጃዎችን ለሚመለከተው አካል በየወቅቱ ያስተላልፋል፤
  • የቢሮውን የኤሌክተሮኒክስና መገናኛ መሳሪያዎችን ደረጃ ያወጣል፣ ግዥ ሲፈጸም በደረጃጀቸው መሠረት መሆኑን ያረጋግጣል፣
  • የቢሮው የኤሌክትሮኒክስና መገናኛ መሳሪያዎች ደህንነት እንዲጠበቁ የጥገናና የስርዓት ማሻሻል ስራዎችን ይሠራል፤
  • ከህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ጋር በመሆን ለማህበረሠቡ የሚቀርቡ መረጃዎችን ያሳልጣል፤
  • ለቢሮው ተጠሪ ለሆኑ ተቋማት ድጋፍና ክትትል ያደርጋል፤
Scroll to Top