የግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ተግባርና ሃላፊነት
- ስለክፍያ በክልልም ሆነ በዞን የመስኖና ድሬኔጅ ጥናትና ዲዛይን ወይም ግንባታ ስራ እንዲያከናውን ኃላፊነት ተሠጥቶች ውል የያዘው አካል በውሉ መሠረት ክፍያዎችን ይፈጽማል፤ በውል አስተዳደሩ ሂደቱ የሚፈተሩ ችግሮችንም በኃላፊነት ይዞ መፍትሄ ይሠጣል፤
- በቢሮው የሚታዘዙ የመስኖና ድሬኔጅ የግንባታና የአማካሪ ክፍያ ሠነዳቸው መሟላቱን እያረጋገጠ በጊዜው ክፍያ ይፈጽማል፤
- በቢሮው የሚታዘዙ ሌሎች ክፍያዎችን መመሪያን መሠረት በማድረግ በጊዜው ክፍያ ይፈጽማል፤
- የሂሳብ የወጭና ገቢ የሂሳብ ሰነዶችን ከውስጥ ኦዲት፣ ከዕቅድ ዝግጅት እና ከባንክ ጋር ይናበባል፣ ሪፖርት አዘጋጅቶ በየ15 ቀኑ ለቢሮ ኃላፊው ያቀርባል፤
- የቢሮውን ንብረትና ተሸከርካሪ በተቀመጠው የአሠራር መመሪያ መሠረት መዝግቦ ይይዛል፣ በየ3 ወሩ ያለውን ንብረት ለቢሮ ኃላፊው በሪፖርት ያሳውቃል፤
- ማንኛውንም ከንብረትና ፋይናስ የተገናኘ ሰነድ በአግባቡ ይሠንዳል፣ ሲጠየቅም ያቀርባል፤
- አጠቃላይ የፋይናንስና ግዥ አሠራር የክልሉን የገንዘብ ቢሮ የአሠራ መመሪያ፣ የፕሮጀክቶችንና የፕሮግራሞችን የሀብት አስተዳደር መመሪያ መሠረት አድርጎ ይፈጽማል፤
- ለቢሮው የሚያስፈልጉ የቁስ እና የአገልግሎት ግዥዎችን ዕቅድ ያዘጋጃል፣ ያፀድቃል፣ መመሪያን መሠረት አድርጎ ግዥ ይፈጽማል፤
- በተቋሙ ውስጥ አገልግሎት የማይሠጡ ቁሶችን ያስጠናል፣ ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን የሚወገዱበትን አግባብ ያመቻቻል፤
- ከፋይናስና ንብረት አስተዳደር ጋር በተገናኝ አዳዲስ የአሰራር ስልቶችን ይነድፋል፣ እንዲተገበሩም ለቢሮ ያቀርባል፤
- ቢሮው የተቋቋመበትን ዓላማ ያሳካ ዘንድ የአሠራር ስርዓት በመዘርጋት የተሽከርካሪ ስምሪት ይሠጣል፤
- የተሸከርካሪ ስምሪት አሠራር እያዘጋጀ በቢሮው ያፀድቃል፤
- የነዳጅ አጠቃቀም ወጪ ቆጣቢ በሆነ መልኩ እንዲፈጸም አሠራር ይዘረጋል፤
- ተሸከርካሪዎች ወቅታዊ ጥገናና ፍተሻ እንዲያገኙ ያደርጋ፣ የክልሉን የመንገድ ትራንስፖርት መመሪያ በሚያዘው መሠረት ሌሎች ተግባሮችን እንዲፈጸሙ ያደርጋል፤
- ለቢሮው ተጠሪ ለሆኑ ተቋማት ድጋፍና ክትትል ያደርጋል፤