የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ተግባርና ሃላፊነት
- አጠቃላይ የተቋም ተግባርና ሃላፊነት እንዲሁም አሰራርና አፈጻጸሞችን ለማህበረሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች መረጃ ይሰጣል፤
- የትኛውም በመንግስት በጀት የሚመሩ የቢሮው መድረኮችና ስልጠናዎች ከቅድመ ዝግጅት ስራዎች ጀምሮ ለመድረኩ ስኬታማነት ሃላፊነት ወስዶ ያስተባብራል፣ እንደ አስፈላጊነቱ የአጋር አካላት መድረኮችን ድጋፍ ያደርጋል፤
- የተጠናቀቁ የመስኖ ግንባታ ርክክቦች እና የምርቃ ስነስርዓቶችን ያስተባብራል፤
- በመረጃ ነጻነት አዋጅ መሰረት ማንኛውም የተቋሙን አሰራር አስምልክቶ ለሚዲያ አካላት እና ለማህበረሰቡ ግልጽ መረጃ የሚያገኝበትን ሁኔታ ያመቻቻል፤
- በየደረጃው መፈታት ያልቻሉ ፕሮጀክቶች ግንባታ ላይ የሚነሱ የማህበረሰብ ቅሬታዎችን እና አቤቱታዎች የሚፈቱበትን መንገድ ያመቻቻል፤
- ቢሮው በሚያከናውናቸው ተግባራት ውስጥ የተሻለ ተሞክሮዎችን በመቀመር እንዲሰፉ የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ስራ ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን ይሠራል፤
- በመስኖና ድሬኔጅ ዙሪያ በማህበረሰቡና በተቋሙ ውስጥ ያሉ ዕውቀቶችንና ልምዶችን በማሰባሰብ ከአዳዲስ አሰራሮችና እውቀቶች ጋር የሚጣመሩበትንና የሚሸጋገሩበትን አግባብ ያስተባብራል፤
- ሌሎች ከመስኖና ድሬኔጅ ጋር የተገናኙ የህትመት ውጤቶችን ለማህበረሠቡ ያደርሳል፤
- ለቢሮው ተጠሪ ለሆኑ ተቋማት ድጋፍና ክትትል ያደርጋል፤